Opposition Voice

Opposition Voice

Friday, May 2, 2014

ጋዜጠኛ ነብዩና የአንድነት ሊቀመንበር ታሰሩ፤ ሌሎችም ታገቱ፤ ቅስቀሳው በበራሪ ወረቀት እና በሸገር ሬድዮ ቀጥሏል




ጋዜጠኛ ነብዩ ሃይሉ የቀስቃሾቹን እንቅስቃሴ ለመዘገብ በወጣበት ለእስር ተዳርጓል፡፡በካዛንቺስ ፖሊስ ጣብያ ከነብዩ ጋር የአዲስ አበባ የአንድነት ሊቀመንበር ዘካሪያስ የማነብርሃንና ዘላለም ደበበ ይገኙበታል፡፡የጣብያው ኃላፊዎች ‹‹ቤተ መንግስት አካባቢ ቀስቅሳችኋል›› የሚል ውንጀላ አቅርበውባቸዋል፡፡
Nebiyu Hailu
በሌላ በኩል ብሮሸርና ፍላየር የሚያሰራጩ ወደ ቦሌ የተጓዙ አባላት መሳይ ትኩ፣ ማቲዎስ አርጉና አያሌው ዳርምያለውን ጃፓን ኤምባሲ (ጤና ጣቢያው) አካባቢ ባለው ፖሊስ ጣቢያ ታግተዋል፡፡
10
እስራቱ እና እንገልቱ ቢጠናከርም ቅስቀሳው ከጽ/ቤት ተነስቶ በ4ኪሎ አሚሪካ አምባሲ፣ መነን ት/ቤት፣ አፍንጮ በር፣ ፒያሣ፣ ቸርቸር ጎዳና፣ ጥቁር አንበሳ፣ ፍልውሃ፣ ቤተመንግስት፣ ሣሪስ፣ አደይ አበባ፣ ላንቻ፣ ጎተራ ተጠናክሮ ቀጥሏል፡፡ ቅስቀሳው ከጽ/ቤት ተነስቶ በ4ኪሎ አሚሪካ አምባሲ፣ መነን ት/ቤት፣ አፍንጮ በር፣ ፒያሣ፣ ቸርቸር ጎዳና፣ ጥቁር አንበሳ፣ ፍልውሃ፣ ቤተመንግስት፣ ሣሪስ፣ አደይ አበባ፣ ላንቻ፣ ጎተራ ተጠናክሮ ቀጥሏል፡፡ የአዲስ አበባ ነዋሪም እሁድ እንወጣለን አይዟችሁ በርቱ በማለት ቀስቃሾቹን እያበረታቱ ሲሆን በተለይ መርካቶዎች ዛሬ ሰልፉን ጀመሩ በማለት የሕዝቡ የከፋ እሮሮ በማሰማት በጩሀት እየገለጹ ነው፡፡
ፖሊስ በመኪና፣ወረቀት በመበተንና ፖስተር በመለጠፍ መቀስቀስ አይቻልም በማለት እስር ይፈጽማል፡፡ቀዳዳዎቹን በሙሉ በመጠቀም አዲስ አበቤን ድምጽህን አሰማ የሚለው አንድነት በሸገር ኤፍ ኢም 102.1 ሬዲዮ ጣቢያ ማስታወቂያ እንዲነገርለት ተገቢውን ክፍያ በመፈጸም የመጀመሪያው ጥሪ ዛሬ እንዲተላለፍ አስደርጓል፡

ምንጭ፡ አቡጊዳ
http://ethioforum.org/%E1%8C%8B%E1%8B%9C%E1%8C%A0%E1%8A%9B-%E1%8A%90%E1%89%A5%E1%8B%A9%E1%8A%93-%E1%8B%A8%E1%8A%A0%E1%8A%95%E1%8B%B5%E1%8A%90%E1%89%B5-%E1%88%8A%E1%89%80%E1%88%98%E1%8A%95%E1%89%A0%E1%88%AD-%E1%89%B3/

No comments:

Post a Comment