Opposition Voice

Opposition Voice

Sunday, April 6, 2014

የደሴው ሰላማዊ ሰልፍ በድምቀት ተካሄደ!




(EMF) ዛሬ መጋቢት 28 ቀን በደሴ የሚደረገውን ሰላማዊ ሰልፍ ያስተባበረው አንድነት ፓርቲ ነው:: የፓርቲው ከፍተኛ አመራር አባላት በትላንትናው እለት ቅስቀሳ እያደረጉ በነበረበት ወቅት ፖሊስ እና ደህንነቶች ቅስቀሳውን ለማስቆም ጥረት አድርገው ነበር:: በተለለይም የከተማው የጸጥታ ዘርፍ ሃላፊ ነው የተባለው ሰው የቅስቀሳ መሳሪያዎችን ጭምር ለመንጠቅ ሙከራ አድርጎ ነበር – ባይሳካለትም::
dessei11
ይህ ሁሉ አልፎ ዛሬ ህዝቡ በነቂስ ወጥቶ በአስተዳደሩ ላይ በተለይም በመሬት ይዞታ ባለቤትነት ጉዳይ እና አላግባብ ስለታሰሩት ኢትዮጵያውያን ድምጹን ከፍ አድርጎ እያሰማ ይገኛል:: ሰላማዊ ሰልፉ እንደተጀመረ ፖሊስ መንገዱን በመዝጋት ሰልፈኛውን ለማወክ ጥረት አድርጎ ነበር:: ህዝቡ ግን ፖሊስን እየጣሰ ሰልፉን በሰላማዊ መንገድ እያደረገ ነው::
በሰልፉ ላይ…
-ዜጎችን ከቀያቸው ማፈናቀል ይቁም
- መሬት ለህዝብ ይመለስ
- ጭቆና በቃን
- ድል የህዝብ ነው
- በግፍ የታሰሩ ይፈቱ
- መሬት ከካድሬው ወደ ህዝቡ ይመለስ
- አንድነት ኃይል ነው
- የፖለቲካ እስረኞች ይፈቱ… የሚሉ መፈክሮች ሲስተጋቡ ነበር::
ለተሰበሰበውም ህዝብ በደሴ የአንድነት ተወካይ በቅድሚያ ንግግር አድርገዋል:: ኢንጂነር ዘለቀ ረዲ እና የአንድነት ፓርቲ ምክትል ፕሬዘዳንት አቶ ተክሌ በቀለ ንግግር አድርገው ሰላማዊ ሰልፉ በኢትዮጵያዊ ጨዋነት ተጠናቋል:: የደሴም ህዝብ ብሶቱን የሚያሰማበት መድረክ በመፈጠሩ ምስጋናውን ለፓርቲው አመራሮች አቅርቧል::

ተጨማሪ ፎቶዎችን ከፓርቲው ምንጮች ስናገኝ በርከት አድርገን እናቀርባለ

http://ethioforum.org/%E1%8B%A8%E1%8B%B0%E1%88%B4%E1%8B%8D-%E1%88%B0%E1%88%8B%E1%88%9B%E1%8B%8A-%E1%88%B0%E1%88%8D%E1%8D%8D-%E1%89%A0%E1%8B%B5%E1%88%9D%E1%89%80%E1%89%B5-%E1%8A%A5%E1%8B%A8%E1%89%B0%E1%8A%AB%E1%88%84/
https://www.blogger.com/blogger.g?blogID=1297224607727894467#editor/target=post;postID=5433038598778201288

No comments:

Post a Comment